October 6 2020
የኮቪድ-19 ክትባት በፈረንጆቹ አቆጣጠር በአመቱ መጨረሻ ላይ ዝግጁ ሊሆን እንደሚችል የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ቴድሮስ አድሃኖም ገልጸዋል፡፡
ክትባቶቹ ሲገኙ እኩል ስርጭት እንዲኖር የሁሉም አገራት መሪዎች አጋርነትና የፖለቲካ ቁርጠኝነት ሊኖራቸው እንደሚገባ ዋና ዳይሬክተሩ ጥሪ አቅርበዋል፡፡
በአለም ጤና ድርጅት የሚመራው የኮቪድ-19 ክትባት በፍትሃዊነት ለማሰራጨት የተቋቋመው ኮቫክስ (COVAX) በሙከራ ደረጃ ያሉ ዘጠኝ ክትባቶች ስኬታማ ከሆኑ 2 ቢሊዮን ክትባቶችን ለማሰራጨት በዝግጅት ላይ መሆኑን ሮይተርስ አስነብቧል፡፡