You are currently viewing የኒውዚላንድ ድል በኮቪድ-19 ላይ!

የኒውዚላንድ ድል በኮቪድ-19 ላይ!

ኒውዚላንድ ያለ ማህበረሰብ ውስጥ ስርጭት ድፍን 100 ቀናትን አስቆጥራለች::

የኒውዚላንድ ጤና ሚኒስቴር እንደተናገሩት በእሁድ ቀን ምንም የኮቪድ-19 አዲስ ታማሚ በሀገሪቱ አልተገኘም:: በሀገሪቱ ውስጥ በአሁኑ ሰአት ኮቪድ-19 ያለባቸው አጠቃላይ ሰዎች ብዛትም 23 ሲሆን ሁሉም በለይቶ ማቆያ ውስጥ ይገኛሉ::

በሀገሪቷ ውስጥ በሽታው ከያዘው ሰው ጋር የንክኪ ታሪክ ያልነበረው አዲስ ታማሚ ከተገኘ ድፍን 100 ቀናት ተቆጥረዋል:: ነገር ግን የሀገሪቱ የጤና ዳይሪክተር ጀነራል ዶክተር አሽሊ ብሉምፊልድ ለስኬቱ እውቅና ቢሰጡም አሁንም ግን ጥንቃቄ እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል:: አክለውም በሌሎች የቫይረሱን ስርጭት በተቆጣጠሩ ሀገራት ቫይረሱ እንደገና በምን ያህል ፍጥነት ሊያንሰራራ እንደሚችል ስላየን ወደፊት ተጨማሪ ኬዞችን እንዳናገኝ መጠንቀቅ አለብን ብለዋል::

ከዚህ ቀደም ኮቪድ-19 ድል መንሳቷን አውጃ የነበረችው ኒውዚላድ ተጨማሪ 2 አዲስ የኮሮናቫይረስ ተጠቂዎችን ከአዋጁ በጥቂት ጊዜ ውስጥ ማግኘቷን ይታወሳል::

ያገኘቻቸው 2ቱም የቫይረሱ ተጠቂዎች ከእንግሊዝ ወደ ኒውዚላንድ ያቀኑ ሲሆን የቀብር ስነ ስርዓት ላይ ለመታደም በልዩ ፍቃድ ወደ ሀገሪቱ የገቡ ነበሩ፡፡

Leave a Reply